Telegram Group & Telegram Channel
ጥያቄ:- ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት ነው? ለምን  ይሰገዳል?

መልስ

ታቦት በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር በምህረት በሚገለጥበት ጊዜ ዙፋኑ ነው፡፡  ከክርስትና በፊት የብሉይ ኪዳን አገር የነበረችው ኢትዮጵያ በክርስትና ጊዜም ከብሉይ ኪዳንም ያገኘቻቸውን ጠቃሚ ነገሮች በክርስትና መንፈስ እየተረጎመች ትጠቀምባቸዋለች፡፡
ከብሉይ ኪዳን የወሰደቻቸው አንዱ ጽላተ ኪዳን ታቦተ ህጉ ነው፡፡ የደብተራ ኦሪት ጽላት እግዚአብሔር በደመና ተከናንቦ ሙሴንና አሮንን የሚነጋግርበት ለእስራኤል ልጆችም በረድኤት የሚገለጥበት ዙፋን ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ታቦት ግን የአምላክ ስጋና ደም የሚፈተትበት ስጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ህይወት አለው፡፡ ስጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ ያመኑትን ሁሉ የሚጠራበት የምህረት ምስዋዕ ነው፡፡ ክብርና ሰግደትም ለዚህ ይደረግለታል፡፡

👉 በርግጥ የሐዲስ ኪዳን ታቦት ከብሉይ ኪዳን ታቦት የሚለይበት መንገድ አለው። በሐዲስ ኪዳን ታቦት የሚባለው የብሉይን ታቦትና ጽላት አንድ አድርጎ የያዘ ይመስላል። በብሉይ ጽላት ላይ  የተጻፉት ቃላትም አልተጻፉበትም። ምክንያቱም በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ቀዳማዊ እንደተገለጸው ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ የሚችል ጻሕልና ጽዋ የሚያስቀምጥ እንዲሆን ተወስኗል። በላዩም አልፋ ወኦ፤ ቤጣ ፤ የውጣ የሚባሉ አስማተ መለኮት (የአምላክ ስሞች) በአራቱ ማዕዘን ይቀረጽበታል። በመካከል ሥነ ስቅለት ይቀረጽበታል። "ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ታቦተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ተብሎ ይጻፍበታል። ኪሩቤል መንበረ ጸባዖትን እንደተሸከሙ ይሳልበታል። ከዚያም የቅዱሱ ስም ይቀረጽበታል። እስከ 15ኛው ምእተ ዓመት ከላይ ቅድስት ሥላሴ
ዝቅ ብሎ እመቤታችን ወደ ላይ አንገቷን በማቅናት ከታች ደግሞ ቅዱሱን ወደ እመቤታችን አቅንተው ይቀረጹ ነበር። ከላይ ታቦቱ ጻሕል ጽዋ እንዲያስቀምጥ ሆኖ የሚሰራው መሰዊያ ሆኖ ስለሚያገለግል ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በዕብ.13:10 ላይ "መሠዊያ አለን" ያለው ታቦቱን እንደሆነ   ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተርጉሞታል። "ታቦት ነበረን" አላለምና ታቦት አለን ያለው በዘመነ ሐዲስ በመሆኑ መሠዊያ በሐዲስ ኪዳን ለመኖሩ ያስረዳል ብሏል... ከዚህ አንጻር የታቦቱ አገልግሎት ለመሠዊያ ነው። መሠዊያ አለን እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ያለ መሠዊያ የምትኖር ቤተ ክርስቲያን የለችም።
[ሁለቱ ኪዳናት ገጽ.310-311፤ መሪጌታ ሐየሎምና ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ]

👉 ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉ እህት አብያተ ክርስቲያናት (Oriental Churches) ታቦት የተለመደ ህግ ነው፡፡ ስጋ ወደሙን የሚፈትቱት በታቦቱ ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ፦ ግብፃውያን ታቦቱን "ሉህ" ይሉታል፡፡ ጽላት ሰሌዳ ማለት ነው፡፡ ያለሱ ስጋ ወደሙ አይፈተትም፡፡ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት "የግሪክ፣ የሩሲያ የሩማንያና" የሌሎችም ወደ ክርስትና የተመለሱት ከአረማዊነት ስለሆነ የታቦትን ምስጢር አያውቁም፡፡ በታቦቱ ፈንታ ከመንበር የማይነሳ እንደ ታቦት የሚከበር የጌታ የስቅለቱ ወይም የግንዘቱ ስዕል ያለበት የነጭ ሐር መጎናጸፊያ አላቸው፡፡ ያለሱ ስጋውን ደሙን አይፈትቱም፡፡ ይህን በጽርዕ "አንዲሚንሲዮን" ይሉታል፡፡ "ህየንተ ታቦት" ማለት ነው፡፡ የሮማ ካቶሊኮች "ሜንሳ " "MENSA" ይሉታል፡፡ ጠረጴዛ ማለት ነው፡፡ [የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፡ አባ ጎርጎርዮስ ገጽ108-110]

👉 ስለዚህም የክርስቶስ ሥጋና ደም የሚፈተትበት ስለሆነ ክብርና ስግደት ይገባዋል። ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጻፈበት ስለሆነ ስለ ስሙ ስግደት ለማቅረብ በታቦት ፊት እንሰግዳለን። ቅዱስ ጳውሎስ ለፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች በላከው መልዕክቱ  "፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥፤ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።" ፊልጵ.2:10-11 እንዳለ በታቦቱ ፊት እንሰግዳለን።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]



tg-me.com/mnenteyiklo/2822
Create:
Last Update:

ጥያቄ:- ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት ነው? ለምን  ይሰገዳል?

መልስ

ታቦት በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር በምህረት በሚገለጥበት ጊዜ ዙፋኑ ነው፡፡  ከክርስትና በፊት የብሉይ ኪዳን አገር የነበረችው ኢትዮጵያ በክርስትና ጊዜም ከብሉይ ኪዳንም ያገኘቻቸውን ጠቃሚ ነገሮች በክርስትና መንፈስ እየተረጎመች ትጠቀምባቸዋለች፡፡
ከብሉይ ኪዳን የወሰደቻቸው አንዱ ጽላተ ኪዳን ታቦተ ህጉ ነው፡፡ የደብተራ ኦሪት ጽላት እግዚአብሔር በደመና ተከናንቦ ሙሴንና አሮንን የሚነጋግርበት ለእስራኤል ልጆችም በረድኤት የሚገለጥበት ዙፋን ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ታቦት ግን የአምላክ ስጋና ደም የሚፈተትበት ስጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ህይወት አለው፡፡ ስጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ ያመኑትን ሁሉ የሚጠራበት የምህረት ምስዋዕ ነው፡፡ ክብርና ሰግደትም ለዚህ ይደረግለታል፡፡

👉 በርግጥ የሐዲስ ኪዳን ታቦት ከብሉይ ኪዳን ታቦት የሚለይበት መንገድ አለው። በሐዲስ ኪዳን ታቦት የሚባለው የብሉይን ታቦትና ጽላት አንድ አድርጎ የያዘ ይመስላል። በብሉይ ጽላት ላይ  የተጻፉት ቃላትም አልተጻፉበትም። ምክንያቱም በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ቀዳማዊ እንደተገለጸው ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ የሚችል ጻሕልና ጽዋ የሚያስቀምጥ እንዲሆን ተወስኗል። በላዩም አልፋ ወኦ፤ ቤጣ ፤ የውጣ የሚባሉ አስማተ መለኮት (የአምላክ ስሞች) በአራቱ ማዕዘን ይቀረጽበታል። በመካከል ሥነ ስቅለት ይቀረጽበታል። "ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ታቦተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ተብሎ ይጻፍበታል። ኪሩቤል መንበረ ጸባዖትን እንደተሸከሙ ይሳልበታል። ከዚያም የቅዱሱ ስም ይቀረጽበታል። እስከ 15ኛው ምእተ ዓመት ከላይ ቅድስት ሥላሴ
ዝቅ ብሎ እመቤታችን ወደ ላይ አንገቷን በማቅናት ከታች ደግሞ ቅዱሱን ወደ እመቤታችን አቅንተው ይቀረጹ ነበር። ከላይ ታቦቱ ጻሕል ጽዋ እንዲያስቀምጥ ሆኖ የሚሰራው መሰዊያ ሆኖ ስለሚያገለግል ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በዕብ.13:10 ላይ "መሠዊያ አለን" ያለው ታቦቱን እንደሆነ   ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተርጉሞታል። "ታቦት ነበረን" አላለምና ታቦት አለን ያለው በዘመነ ሐዲስ በመሆኑ መሠዊያ በሐዲስ ኪዳን ለመኖሩ ያስረዳል ብሏል... ከዚህ አንጻር የታቦቱ አገልግሎት ለመሠዊያ ነው። መሠዊያ አለን እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ያለ መሠዊያ የምትኖር ቤተ ክርስቲያን የለችም።
[ሁለቱ ኪዳናት ገጽ.310-311፤ መሪጌታ ሐየሎምና ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ]

👉 ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉ እህት አብያተ ክርስቲያናት (Oriental Churches) ታቦት የተለመደ ህግ ነው፡፡ ስጋ ወደሙን የሚፈትቱት በታቦቱ ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ፦ ግብፃውያን ታቦቱን "ሉህ" ይሉታል፡፡ ጽላት ሰሌዳ ማለት ነው፡፡ ያለሱ ስጋ ወደሙ አይፈተትም፡፡ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት "የግሪክ፣ የሩሲያ የሩማንያና" የሌሎችም ወደ ክርስትና የተመለሱት ከአረማዊነት ስለሆነ የታቦትን ምስጢር አያውቁም፡፡ በታቦቱ ፈንታ ከመንበር የማይነሳ እንደ ታቦት የሚከበር የጌታ የስቅለቱ ወይም የግንዘቱ ስዕል ያለበት የነጭ ሐር መጎናጸፊያ አላቸው፡፡ ያለሱ ስጋውን ደሙን አይፈትቱም፡፡ ይህን በጽርዕ "አንዲሚንሲዮን" ይሉታል፡፡ "ህየንተ ታቦት" ማለት ነው፡፡ የሮማ ካቶሊኮች "ሜንሳ " "MENSA" ይሉታል፡፡ ጠረጴዛ ማለት ነው፡፡ [የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፡ አባ ጎርጎርዮስ ገጽ108-110]

👉 ስለዚህም የክርስቶስ ሥጋና ደም የሚፈተትበት ስለሆነ ክብርና ስግደት ይገባዋል። ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጻፈበት ስለሆነ ስለ ስሙ ስግደት ለማቅረብ በታቦት ፊት እንሰግዳለን። ቅዱስ ጳውሎስ ለፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች በላከው መልዕክቱ  "፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥፤ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።" ፊልጵ.2:10-11 እንዳለ በታቦቱ ፊት እንሰግዳለን።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]

BY ምን እንጠይቅሎ?


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/mnenteyiklo/2822

View MORE
Open in Telegram


ምን እንጠይቅሎ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In many cases, the content resembled that of the marketplaces found on the dark web, a group of hidden websites that are popular among hackers and accessed using specific anonymising software.“We have recently been witnessing a 100 per cent-plus rise in Telegram usage by cybercriminals,” said Tal Samra, cyber threat analyst at Cyberint.The rise in nefarious activity comes as users flocked to the encrypted chat app earlier this year after changes to the privacy policy of Facebook-owned rival WhatsApp prompted many to seek out alternatives.ምን እንጠይቅሎ from pl


Telegram ምን እንጠይቅሎ?
FROM USA